Watch Fana TV (FBC) Live from Ethiopia

Fana TV is a commercial television station that broadcasts news and current affairs programs.
It is owned by Fana Broadcasting Corporate (FBC) an Amharic-language radio and television station headquartered in Addis Ababa.

Website: https://www.fanabc.com/
Live stream Fana TV (FBC): https://www.fanabc.com/live


ተቋማችን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በ1987 ዓመተ ምህረት ሲቋቋም በኃላ ቀር መሳሪያዎችና በጥቂት የሰው ሃይል በሀገራችን የብሮድካስት ሚዲያ አዲስ አቀራረብ ይዞ ወደ ስራ ገባ። በሂደትም አደረጃጀቱንና የፕሮግራም ይዘቱን እያሻሻለና ችግሮቹን እየቀረፈ ገስጋሴዉን ቀጠለ። ህብረተሰብ ተኮር ፕሮግራሞች ላይ በማጠንጠን የሚታወቀውና ለህዝባችን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ኑሮ መሻሻልና መዳበር የሚተጋው የሚዲያ ተቋማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ አድማጮቹን እና ተመልካቾቹን እንዲሁም ተባባሪዎቹን ያበረከተ በቴሌቪዥን፣ ሬዲዮና ኦንላይን ዘርፍ በከፍተኛ ደረጃ ተመራጭ እየሆነ መጥቷል።

ተቋማችን ራሱን በተማረ እና ልምድ ባካበተ የሰዉ ሃይል ያሟላና ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር ያዋሃደ የማስተማር፣ የማሳወቅና የማዝናናት ሚናዉን አጠናክሮ በመቀጠል በሀገራችን ሚዲያ ለውጥ ማምጣቱን ቀጥሏል። በሬዲዮ እና በኦንላይን የሚዲያ ዘርፍ የረዥም ጊዜ ልምድን ያካበተው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በሀገራችን ታሪክ ለሚዲያ ተብሎ የተሰራ ባለ 11 ፎቅ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ህንፃ ባለቤት በመሆን ከሀገራችን አልፎ በምስራቅ አፍሪካ ግንባር ቀደም የሚዲያ ተቋም የመሆን ህልሙን ለማሳካት ከጥር 2003 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አድጎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።

ባስገነባው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ሙሉ በሙሉ ኤች ዲ/HD/ የሆነ የቴሌቪዥን ስቱዲዮ በመገንባትም በሀገሪቱ ታሪክ ሙሉ በሙሉ ኤች ዲ የሆነ የቴሌቪዥን ስርጭት በመጀመር ፈር ቀዳጅ መሆን ችሏል። ተቋሙ ከወራት የሙከራ ስርጭት በኋላ 2010 ጥር ወር ላይ በይፋ በኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾሙ የቴሌቪዥን ጣቢያውን በማስመረቅ በሙሉ አቅሙ በአማርኛ ቋንቋ ወደ ስርጭት ገብቷል።

ዘመኑ በሚጠይቀው የኦንላይ ሚዲያ ዘርፍም ራሱን በሰው ሀይል እና በቁሳቁስ በማስታጠቅ በአማርኛ፣ ኦሮሚኛ፣ ትግረኛ እና ኢንግሊዘኛ ቋንቋዎች በድረገፅ በኩል የዲጂታል ይዘትን በማሰራጨት ላይ ይገኛል። በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን በብዛት በሚጠቀሟቸው የፌስቡክ እና ትዊተር የማህብራዊ ትስስር ገፆች የዲጂታል ይዘትን በፅሁፍ፣ በፎቶግራፍ፣ በቪዲዮ እና በድምፅ በማቅረብ ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ በአማካይ በሳምንት እነዚህ የዘቶች ከ6 ሚሊየን የሚበልጥ ጎብኚን በመድረስ ላይ ይግኛሉ።

በሬደዮ ዘርፍም በብሄራዊ ስርጭትና ፋና ኤፍ ኤም 98 ነጥብ 1 በተጨማሪ በብሮድካስቲንግ ሚዲያ ልዩነት በመፍጠር በሀገራችን የሚዲያ ታሪክ በሚያስገርም ፍጥነት ከአዲስ አበባ ውጪ በ11 የክልል ከተሞች የኤፍ̣.ኤም ጣቢያችን የተሟላና በተደራጀ የሰው ሃይልና የሬድዮ ቴክኖሎጂ በማሟላት እርስ በራስ በማስተሳሰር ከፍቷል። በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ 12 የኤፍ̣.ኤም ጣቢያዎች ተቋቁመዋል። አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ አፋርኛ፣ ሶማሊኛ፣ ትግረኛ፣ ወላይትኛ እና ሲዳምኛ የስርጭት ቋንቋዎቹ ናቸው።የራሱን የቴክኖሎጂ፣ ጋዜጠኝነትና ኮሙዪኒኬሽን የስልጠና ማዕከልንም በማቋቋም የስልጠናና እና የማማከር አገልግሎት በመሰጥት ላይም ይገኛል።

በአሁኑ ወቅት ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በማዕከል እና በክልል በአጠቃላይ 1 ሺህ የባለቤትነት መንፈስና የህዝብ ወገንተኝነት ያላቸው ሰራተኞች አሉት።

Other TV channels in the section

Watch Tigrai TV Live from Ethiopia

Tigrai TV (Tigray TV) is a regional television station owned by Tigrai Mass Media Agency, located in Mek’ele (Mekele), Tigray Region. News videos can be viewed on its official YouTube website. Website: http://www.tmma.gov.et/ Live stream Tigrai TV: http://www.tmma.gov.et/live

Read more

Watch Addis TV Live from Ethiopia

Addis TV is a regional public television station owned and operated by Addis Ababa Mass Media Agency (AAMMA). Live streaming can be viewed on its TV’s main page. Website: http://amn.gov.et/ Live stream Addis TV: http://amn.gov.et/live

Read more

Watch Walta TV Live from Ethiopia

Walta TV is a privately owned television station that broadcasts news, entertainment, music, and sports programs. It is owned by Walta Media and Communication Corporate, located in Addis Ababa. Website: https://waltainfo.com Live stream Walta TV: https://waltainfo.com/livestreaming/

Read more

Watch EBC TV Live from Ethiopia

Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC) is the state-owned broadcaster headquartered in Addis Ababa. It operates three channels: EBC 1, EBC 2, and EBC 3. News videos can be viewed on its official YouTube website. Website: http://www.ebc.et/ Live stream EBC TV: http://www.ebc.et/live

Read more

Watch Amhara TV Live from Ethiopia

Amhara TV is a regional public television station based in Bahir Dar, Amhara Region. It is owned by Amhara Mass Media Agency (AMMA). Live streaming and news videos are available on its website. Website: https://www.amharaweb.com/ Live stream Amhara TV: https://www.amharaweb.com/live...

Read more